Facebook Telegram Youtube TikTok TikTok

Dean Office

blog

Participating @MOLS ISO Certification Ceremony

ለጎንደር ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ማህበረሰብ፣ ለጎንደር ከተማ አስተዳደር እና ለአብክመ ስራና ክህሎት ቢሮ እንኳን ደስ ያላችሁ !!

ኮሌጁ የISO 21001:2018 EOMS አለም አቀፍ የትምህርት ጥራት ስታንዳርድ ሰርቲፋይ መሆን ችሏል።

        ### /// ###

ኢተምድ ለስድስት ድርጅቶች የሥራ አመራር ሥርዓት ሰርተፊኬቶችን ሰጠ።

ነሃሴ 28 ቀን 2017 ዓ.ም 

አዲስ አበባ (ኢተምድ)

================================================================================

የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት ለጎንደር ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በትምህርት ስራ አመራር ስርዓት (ISO 21001) ሰርተፊኬቶች ሰጥቷል። ኮሌጁ በሥራ አመራር ሥርዓቶች ዓለም አቀፍ መመዘኛዎችን መሟላታቸውን በተከናወነላቸው የኦዲት ሂደት ተገምግሞ የተሰጣቸው ሲሆን ሰርተፍኬቱን የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ክብርት ኢ/ር መዓዛ አበራ ለድርጅቶቹ የሥራ ኃላፊዎች አስረክበዋል፡፡ 


በሰርተፍኬቱ ርክክብ ወቅት የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ክብርት ኢ/ር መዓዛ አበራ በቅድሚያ የእንኳን ደስአላችሁ መልእክት በማስተላለፍ በዓለም አቀፍ የስራ አመራር ስርዓቶች ሰርተፍኬት ማግኘታቸው ለሚሰጡት አገልግሎት በሀገር ውስጥና በዓለምአቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪና ተመራጭ እንዲሆኑ አስቻይ መሆኑን አብራርቷል። አክለውም የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት የሚሰጣቸውን አገልግሎቶች እንዲሁም አጠቃላይ ስለ ጥራት መንደር ገለፃ በማድረግ ቀጣይ የጋራ ስራዎች ላይ ውይይት ከድርጅቶቹ የስራ ኃላፊዎች ጋር አድርገዋል፡፡

.

blog

GPTC Board Meeting

ቀን 24 /04 / 2018 ዓ/ም
የጎንደር ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የትም/ስልጠና ቦርድ በክህሎት መር ስራ እድል ፈጠራ፣ በአዲሱ የዘርፉ ኢኒሸቲቦች፣ የኮሌጅን አቅም በሚያጠናክሩ የውስጥ ገቢ ማመንጫ የኢንተር ፕራይዝ ስራዎች ላይ ሰፊ ውይይት በማድረግ በቀጠይ ኮሌጁን በመደገፍ ያለበትን የመሠረተ ልማት ችግሮች ለመፍታት አቅጣጫ ተቀመጠ ።

የቦርድ ስብሳቢዎ ክብርት ወ/ሮ ደብሬ የኋላ ኮሌጅ በከተማችን እና ለቀጠናው ፋይዳው ከፍ ያለ በመሆኑ የተሟላ ድጋፍ በማድረግ በዘርፉ የክህሎት ልማት የተጣለበትን ሃላፊነት በብቃት እንዲወጣ ማድረግ ያስፈልጋል ብለዋል ። በተጨማሪም በቀጣይም ከከተማ አስተዳደሩ ሰፋፊ ስራዎችን እየወሰደ የውስጥ አቅሙን የሚያጠናክር ይሆናል ብለዋል ። 

ኮሌጁ በ2017 ዓ/ም የተሻለ አፈፃፀም በማምጣት በክልል ደረጀ እውቅና የተሰጠው እና በኢትዮጵያ ተሰማሚነት ምዘና ድርጅት በISO 21001:2018 EOMS ሰርቲፋይድ የሆነ ተቋም ሲሆን በቀጣይ ይህን ውጤት ማስቀጠል እንዳለበት የቦርድ አባላት አሳስበዋል ።

ጎፓቴኮ !
.