Foundation and Early Years as Skill Development Center (1989 E.C. - 1993 E.C.) Gondar Polytechnic College traces its origins to 1989 Ethiopian Calendar (E.C.), founded as the Skill Development Center in the Amhara Region, Ethiopia. At establishment, the center... Read more
ለጎንደር ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ማህበረሰብ፣ ለጎንደር ከተማ አስተዳደር እና ለአብክመ ስራና ክህሎት ቢሮ እንኳን ደስ ያላችሁ !!
ኮሌጁ የISO 21001:2018 EOMS አለም አቀፍ የትምህርት ጥራት ስታንዳርድ ሰርቲፋይ መሆን ችሏል።
### /// ###
ኢተምድ ለስድስት ድርጅቶች የሥራ አመራር ሥርዓት ሰርተፊኬቶችን ሰጠ።
ነሃሴ 28 ቀን 2017 ዓ.ም
አዲስ አበባ (ኢተምድ)
================================================================================
የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት ለጎንደር ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በትምህርት ስራ አመራር ስርዓት (ISO 21001) ሰርተፊኬቶች ሰጥቷል። ኮሌጁ በሥራ አመራር ሥርዓቶች ዓለም አቀፍ መመዘኛዎችን መሟላታቸውን በተከናወነላቸው የኦዲት ሂደት ተገምግሞ የተሰጣቸው ሲሆን ሰርተፍኬቱን የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ክብርት ኢ/ር መዓዛ አበራ ለድርጅቶቹ የሥራ ኃላፊዎች አስረክበዋል፡፡
በሰርተፍኬቱ ርክክብ ወቅት የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ክብርት ኢ/ር መዓዛ አበራ በቅድሚያ የእንኳን ደስአላችሁ መልእክት በማስተላለፍ በዓለም አቀፍ የስራ አመራር ስርዓቶች ሰርተፍኬት ማግኘታቸው ለሚሰጡት አገልግሎት በሀገር ውስጥና በዓለምአቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪና ተመራጭ እንዲሆኑ አስቻይ መሆኑን አብራርቷል። አክለውም የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት የሚሰጣቸውን አገልግሎቶች እንዲሁም አጠቃላይ ስለ ጥራት መንደር ገለፃ በማድረግ ቀጣይ የጋራ ስራዎች ላይ ውይይት ከድርጅቶቹ የስራ ኃላፊዎች ጋር አድርገዋል፡፡
Visitors Count:
Courses Uploaded
People certifie
Technical Trainers